የአማራ ማህበር በቤኤርያ (አማቤ) 


መተዳደሪያ ደንብ / ፳፻፲፭            



መግቢያ 


የአማራ ህዝብ መዋቅራዊ በሆነ ግፍ እና አይን ያወጣ የዘር ማጥፋት ወንጀል በሀገራችን በኢትዮጵያ  እየተፈጸመበት ይገኛል። በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖረው የአምሓራ ህዝብ የምግብ ዋስትና የሌለው፤  በንጹህ  የመጠጥ ውሃ እጥረት  የሚሰቃይ ፤  የመሠረታዊ  ትምህርት  ተደራሽነት የሌለው ሲሆን፤ ለከፍተኛ ድህነት ፤ ለጦርነት እና ለእርስ በርስ ግጭት ፤  በሀገር ውስጥ መፈናቀል እና ለውጭ ሀገር ስደት ተዳርጓል። እንዲሁም  የመምረጥ እና የመመረጥ መብቶቹን በመግፈፍ፤ ሆን ተብሎ ከስልጣን እንዲገለል በማድረግ፤ ፍትሃዊ የሃብትና የንብረት ባለቤት እንዳይሆን በተደራጀና በተጠና መዋቅር ሲሰራበት ቆይቷል።  ባጠቃላይ የአማራ ሀዝብ በተደጋጋሚ ጦርነት ኢኮኖሚው እንዲወድም ተደርጎበታል።  ይህ የአምባ ገነን ሥርዐት በአማራ ወገኖቻችን ላይ የከፈተውን የህልውና ጦርነት ለአለም መንግስታት በማሳወቅ እና የአማራን ህዝብ ለነጻነት፣ለእኩልነት፣ ለለፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እና አካታች ሐገራዊ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ፤ በጉልበትና በሀይል የተወሰዱ የአማራውን እርስት ለማስመለስ በሚደረገው የሰላማዊ ትግል መሳተፍና ማገዝ ወቅታዊ እና ቸል ሊባል የማይገባው መሆኑን ተረድተናል።  


በመሆኑም የአማራ ህዝብ ነጻነት በገጠመው የህልውና ፈተና ላይ የራሳችንን አስተዋፅኦ ለማበርከት፤ መላው የአማራ ተወላጅ የሆነ ሁሉ ከጎጥ ከፆታና ከሀይማኖት ልዩነት ሳይገድበው የአማራ ህዝብ በኢትዩጵያ ማህበራዊ፣ እኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮችን ለዘለቄታ መፍትሄ ለማምጣት እንዲያግዝና ከድህነት ለማላቀቅ በሚደረግ ጥረት ሁሉ እንዲተባበር በማመን፤  የሚመሰረተው የቤይ ኤርያ የአማራ ማህበር አሁን ኢትዮጵያን ከሚገዛው የብልፅግና ፓርቲ እንዲሁም ከአማራ ብልፅግና ፓርቲ ተጽዕኖ የፀዳ፤  በሚታመኑ እውነተኛ የአማራ ተዋላጆች በሚመርጠው አመራር በሚያስቀምጠው ግብና በሚነድፈው ዕቅድ እንዲንቀሳቀስ አና እንዲመራ ፤ የቤይ ኤርያ የአማራ ማህበረሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግለት በማመን፣ የቤይ ኤርያ የአማራ ማህበር ሰኔ ፲, ፳፻፲፭ ዓ.ም. (June 17, 2023) በኦክላድ ከተማ፤ በካሊፎርኒያ ጠቅላይ ግዛት ተቋቋመ። 


አንቀጽ 1፡ የማህበሩ ስያሜ


የማህበሩ  ስም/ስያሜ ከዚህ በኋላ "የአማራ ማህበር  በቤይ ኤርያ" ወይም "አማቤ" ወይም Amhara Association of Bay Area ወይም (AABA) ተብሎ ይጠራል። 


አንቀጽ 2፡ የማህበሩ አርማ

የአማራ ማህበር በቤይ ኤርያ የድርጅት አርማ ንስር አሞራ ነው። ንስር አሞራ ፀሐይን ቀጥ ብሎ ማየት የሚችል ወደ ጸሐይ አቅጣጫ ጨረሩን እያየ መብረር የሚችል ብቸኛው የአለማችን ፍጥረት ነው ።  በተጨማሪም ንስር አሞራ ከሰው አይን 8 እጥፍ የተሻለ ማየት ይችላል። በተጨማሪም ንስር አሞራ ከ360° በአንድ እይታ ማየት የሚችል ድንቅ ፍጥረት ነው።  በዚህ ምክንያት ንስር አሞራን የአማራን ህዝብ አርቆ አሳቢነት ስለሚያመለክት፤ የድርጅቱ አርማ ሆኖ ተመርጧል። የአማራ ህዝብ በእውነትም አርቆ አሳቢ ነው፤ ለዘመናት ያጎለበተው የጀግንነት፤ የፍትሀዊ ፤ ሁሉንም በእኩል የማየት እሴቱን እና የአስተሳስብ ብቃቱን ያሳያል።  


አንቀጽ 3፡ አድራሻ


Amhara Association of Bay Area

1319 Washington Avenue Unit 551

San Leandro, CA 94577

Zelle donation: amharabayarea@gmail.com



አንቀጽ 4፡ የደንቡ ተፈጻሚነት


ይህ የአማራ ማህበር ቤይ ኤርያ መተዳደሪያ ደንብ በሰሜን አሜሪካ፣ በካሊፎርንያ ቤይ ኤርያ በሚኖሩ የማሀበሩ አባላት ላይ ተፋጻሚ ይሆናል:: "የአማራ ማህበር በቤይ ኤርያ" ማለት በዚህ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ኦክላንድ ፤ ካሊፎርኒያ  ሰኔ , ፳፻፲፭ .. (June 17, 2023) ዓ/ም የተቋቋመው ቦርድ - መር ድርጅት ነው።


አንቀጽ 5 ፡ ምዝገባ

   

ማህበሩ በአሜሪካ የማህበራት ማቋቋሚያ ህግ 501(C)(3) መሰረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ሆኖ ተመዝግቧል።


አንቀጽ 6፡ የማህበሩ ራዕይ 


የአማራ ህዝብ የማህበራዊ ፤ ኢኮኖሚያዊ፤ የህልውና ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አስተማማኝ ድርጅት ሆኖ ማየት። 


አንቀጽ 7፡  የማህበሩ ተልዕኮ


1. በቤይ ኤርያ የሚኖሩትን የዐማራ ማኅበረሰብ ኅብረት እና አንድነት ማጠናከር፤

2. የዐማራን ሕዝብ ባህል በቤይ ኤርያ አካባቢ ማጎልበት እና ማስተዋወቅ፤

3. በቤይ ኤርያ አካባቢ የሚኖረውን የዐማራ ማኅበረሰብ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊ ኑሮ፣ በሥራ መስክ እና በትምህርት ዘርፍ እርስ በእርስ የሚረዳዳበትን መርኃ ግብሮች መዘርጋት፤

4. የቤይ ኤርያ የዐማራ ማኅበረሰብ በአካባቢው ባለው የዐማራ ጉዳይ ትኩረት የሚሰጠው እንዲሆን እና ተሰሚነት እንዲያገኝ ተፅዕኖ መፍጠር ናቸው።


አንቀጽ 8፡  የማህበሩ አላማ




አንቀጽ 9፡ የቤኤርያ መደበኛ አባላት


የአማራ ማህበር  በቤኤርያ ፤ የአማራን ማህበራዊና አኤኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመቅረፍና ለችግር የተጋለጠውን ወገናችንን ኑሮ በዘላቂነት ሊያሻሽሉ የሚችሉ ፕሮጄክቶችን ፤ የቤኤርያ አማራ አባል በመሆን በቋሚነት በገንዘብም ሆነ በእውቀት እንዲረዱ ያንቀሳቅሳል፣ ያበረታታል። ድጋፋቸውንም ለማበረታታት በመደበኛ እና በክብር አባልነት ይመዘግባል።


2.1. አማራ የሆነ እና በአማራነት መደራጀትን የተቀበለ፤

2.2 የማህበሩን አላማ፣ ግብ፣ፖሊሲና የሚያስቀምጣቸውን ግዴታዎች የሚቀበል፤

2.3 እድሜው ከ18 ዓመት በላይ የሆነ፣ የድርጅቱ የመተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በቦርዱ እና በስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በየጊዜው የሚወጡ የሥነ-ምግባር ደንቦችን የሚቀበልና ተግባራዊ የሚያደርግ፣

2.4 በቦርድ አባላት ( በጠቅላላ ጉባኤ የተወሰነውን ወርሀዊ ክፍያና መዋጮ የሚከፍል)።  በየጊዜው ስምምነት የሚደረግባቸውን ክፍያዎችና መዋጮዎች መክፈል የሚችል፤

2.5 በህግ መብቱ ያልተገፈፈ፡፡


አንቀጽ 10፡ የክብር አባላት



አንቀጽ ​11፡  የአባልነት​ ​መብት  



አንቀጽ​ 12፡  ​የአባልነት​ ​ግዴታ  



አንቀጽ 13፡ የአባላት መዋጮና ሌሎች ክፍያዎች


የማህበሩ  መዋጮና ሌሎች ክፍያዎች የሚደረጉበትን ጊዜና መጠን በጠቅላላ ጉባኤ አባላት ይወሰናል።


አንቀጽ 14፡ ከማህበሩ  አባልነት ስለመሰናበት




አንቀጽ 15፡ የአማራ ማህበር በቤኤርያ አደረጃጀት

 

የአማራ ማህበር  በቤኤርያ አስተዳደር ሦስት ዋና ዋና አካላት ይኖሩታል። 

ጠቅላላ ጉባኤ ፤ የቦርድ አባላት እና የስራ አስጊያጅ ኮሚቴ ናቸው። 




አንቀጽ 16፡ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት 


የአማራ ማህበር  በቤኤርያ አባል የሆነ ሁሉ ስራውን በሙያዊ ብቃት፣ በታማኝነት እና በከፍተኛ የስነ ምግባር ደረጃ ማከናወን አለበት። 


አንድ (የአማቤ)  አባል ፤ የአማራ ህዝብ አሁን ባለው እና ቀድመው በነበሩት አገዛዞች ሆን ተብሎ በሚደርሱ ችግሮች እየተገደለ ፣ እየተሰደደ ፣ እርስቱ እየተወሰደ ፣ እምነት እና ባህሉን እንዳያከብር እየተደረገ ፣ የእምነት ቦታዎቹ  እየወደሙ እንዳለ የተረዳ ፣ ወደስልጣን እንዳይመጣ እየተደረገ ፣ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል እየደረሰበት እንደሆነ የተረዳ መሆን አለበት። በተጨማሪም አባሉ የአማራ ማህበር  በቤኤርያን መተዳደሪያ ደንብ እንዳነበበ እና እሱ ወይም እሷ በመተዳደሪያው እንደሚመሩ ወይም እንደሚታዘዙ ማረጋገጥ አለባቸው።


የማህበሩን መተዳደሪያ ደንብ አንብቤና ተረድቼው ስላመንኩበት ይህን የመተዳደሪያ ደንብ እቀበላለሁ።

ሙሉ ስም፡ ________________________________________ ፊርማ፡ _________________________ ቀን፡_____________________

Full Name: _______________________________________ Signature: _______________________ Date: _____________________

 

አንቀጽ 17፡ የጠቅላላ ጉባኤው ስልጣንና እና ተግባር







አንቀጽ 18፡ የቦርድ ስልጣንና ተግባር


በዚህ መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም በጠቅላላ አባል ጉባኤ በተሰጠው ስልጣን ማንኛውንም የስራ አስካያጅ ኮሚቴ ተግባር እና ስልጣን ለመሾም ለመሻር ተፈቅዶለታል። ቦርዱ በዚህ መተዳደሪያ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠቅላላ ጉባኤው ይሆናል። የማህበሩ የዳይሬክተሮች  የቦርድ ፕሬዝደንት ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ፣ ፀሀፊ ፣ የህዝብ ግንኙነት እና የውስጥ ኦዲተር በአጠቃላይ አባልነት የሚመረጡ እና የሚያገለግሉ ናቸው። እያንዳንዱ የቦርድ ኦፊሰር ስልጣን ይኖረዋል እና ከዚህ በታች የተቀመጡትን ተግባራት ያከናውናል:: 


 

አንቀጽ 19፡ የቦርድ አባላት የስራ ዘመን




አንቀጽ 20፡ መወገድ እና መልቀቂያ

የቦርድ አባላት እንዲሁም የስራ አስካያጅ ኮሚቴ አባላት ስራቸውን በአግባብ ካላከናወኑ ወይም የመስራት ብቃት ከጎደላቸው በዚህ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት በተገቢ ሂደት ከስራቸው ይሰናበታሉ።  

20.1  ጠቅላላ ጉባኤ አባላት ብቁ ባልሆነ የቦርድ አባላት ላይ ተገቢ ሂደት ያካሄዳል። 

20.2  የስራ አስኪያጅ ኮሚቴው ብቁ ባልሆነ የኮሚተው አባል ላይ በሰብሳቢው የበላይ ተመልካችነት የቃል እና የፁህፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ ይወስዳል። ከስራ አስኪያጅ ኮሚቴው አቅም በላይ ሲሆን ወደ ቦርዱ  ያስተላልፋል። 

20.3 የቦርድ አባላት ወይም የስራ አስካያጅ ኮሚቴ አባል በገዛ ፈቃዱ ማህበሩን መልቀቅ ከፈለገ ቢያንስ ከ 2 ወራት በፊት ለማህበሩ ማሳወቅና በወቅቱ በእጁ ላይ ያለ ማንኛውንም ዓይነት የማህበሩን ንብረት ማስረከብ፤ እየሰራ ያለው ትኩረት የሚያስፈልገው ፕሮጀክት ወይም ስራ ካለ ቢቻል አጠናቅቆ ካልሆነም በቅንነት ለሚወከለው ሰው አስተላልፎ ይለቃል።


አንቀጽ 21፡ የቦርድ አመራር አካላት ስልጣንና ተግባራት


 

21.1. የቦርዱ ሰብሳቢ



21.2. ምክትል ሰብሳቢ


21.3. ፀሐፊ


21. 4. የሕዝብ ግንኙነት

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው ሁሉንም የፕሬስ መግለጫዎች ሙሉ በሙሉ ያስተባብራል; በAAB የቦርድ ኃላፊዎች እና በመገናኛ ብዙሃን መካከል ቃለ መጠይቅ ያዘጋጃል። የህዝብ ግንኙነት  ሁሉንም የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችን ጨምሮ በህትመት፣ በኢንተርኔት፣ በሬዲዮ፣ በቲቪ እና በሌሎች ሚዲያዎች በኩል ማስተዋወቂያዎችን ያስተዳድራል።


21.5. የውስጥ ኦዲተር


የሂሳብ ክፍያ፣ ቼኮች፣ የገንዘብ ዝውውሮች፣ ወዘተ ጨምሮ ሁሉንም የፋይናንሺያል መረጃዎች የመመርመር ሃላፊነት ያለው ኦዲተሩ ነው።ኦዲተሩ ይከታተላል እና በጀቱን ያዘጋጃል። ኦዲተሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ የኦዲት ሪፖርቶችን ለዲሬክተሮች ቦርድ ያቀርባል ኦፕሬሽንን ለማሻሻል እና ለድርጅቱ የተሻለ የፋይናንስ አቋምን ያቀርባል።


አንቀጽ 22፡ የቦርድ ስብሰባ


አንቀጽ 23: የቦርድ ድምጽ አሰጣጥ




አንቀጽ 24፡ የሥራ አስኪያጅ ተግባርና ኃላፊነት


የማህበሩ  ሥራ አስኪያጅ ተጠሪነቱ ለቦርድ ሆኖ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል፥

ቦርዱ በሚሰጠው መመሪያ መሠረት፤


አንቀጽ 25፡ የስራ አስካያጅ ኮሚቴ የስራ ዘመን 





   25.1 ዋና ሰብሳቢ (ሊቀመንበር) 



25.2 ምክትል ሰብሳቢ (ም/ሊቀመንበር)



25.3 ፀሐፊ


 ፀሐፊው ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤



አንቀጽ 26: የሂሣብ ሓላፊ ተግባርና ኃላፊነት


ሂሣብ ሐላፊ ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤


አንቀጽ 27፡ ገንዘብ ያዥ


ሂሣብ ሐላፊ ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤ ቦርዱ ፤  የአማራ ማህበር በቤኤርያ  ትሬዠር ሆኖ የሚያገለግለውን የገንዘብ ተቋም ወይም ባንክ የሚወስን ሲሆን ገንዘብ ያዡ የሚከተሉትን ተግባራት ያከናውናል፥


አንቀጽ 28፡ የሶሻል ሚዲያ እና የኢቬንት ዳይሬክተር


የሶሻል ሚዲያ እና የኢፌንት ዳሬክተር ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤



አንቀጽ 29፡ የአድፎከሲ እና የኮሚኒቴ ኢንጌጅመንት ዳይሬክተር


የአድፎከሲ ዳይሬክተር እና የኮሚኒቴ ኢንጌጅመንት አላፊ ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤


አንቀጽ 30፡ ም/ የአድፎከሲ ዳይሬክተር እና የኮሚኒቴ ኢንጌጅመንት አላፊ



አንቀጽ 31፡ የህዝብ ግኑኝነት

የህዝብ ግኑኝነት አላፊ ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤



31.1፡ ም/ የህዝብ ግኑኝነት ሀላፊ


ም/ የህዝብ ግኑኝነት አላፊ ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል።




አንቀጽ 32፡ የጥናት፣ የትምህርት፤ እንዲሁም የምርመራ ጥናት ኮሚቴ ሀላፊ


የጥናት እና የምርምር የስራ ሒደት ሀላፊነቱ ተጠሪነቱ ለዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የሚከተሉት ተግባራትና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፤



አንቀጽ 33: የስራ አስካያጅ ኮሚቴ ስብሰባ 



አንቀጽ 34: የቦርድ ምልመላና አተካክ ሥነ-ሥርዓት


   

አንቀጽ 35፡ አጋር ማህበራት


  

አንቀጽ 36፡ የገንዘብ አጠቃቀም



አንቀጽ 37፡ ሕገ- ወጥ የገንዘብ ዝውውር ድርጊትን መከላከል



አንቀጽ 38፡ ግልፅነትና ተጠያቂነት



አንቀጽ 39፡ የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ስለማሻሻል



አንቀጽ 40፡ የማህበሩ መዋሃድና መለወጥ



አንቀጽ 41፡ ስለማህበሩ መፍረስ



አንቀጽ 42፡ ይህ የመተዳደሪያ ደንብ የሚጸናበት ጊዜ